Posted in Bloggies on January 03, 2012 by
በአዳነ ደቻሣ
0911- 43- 6941
This e-mail address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it
ግብረሰዶማዊነትና ቤተክርስቲያን
የግብረሰዶማዊነት ጽንሰ ሀሳብ ሰለጠነ በተባለው ዓለም ወደ ኅበረተሰቡ እየሰረጸና ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ በመምጣቱ፤ ቤተክርስቲያንም ለዚህ ጉዳይ አዎንታዊ ምላሽ እንድትሰጥ የጉዳዩ አቀንቃኞች በቤተክርስቲያን ላይ ከፍተኛ ጫና በማሳደር ላይ ይገኛሉ፡፡ ጫና ማሳደር ብቻ ሳይሆን ጉዳዩ መጽሐፍ ቅዱሳዊና እግዚአብሔርም የተቀበለው እንደሆነ ለማረጋገጥ ከመጽሐፍ ቅዱስ ያጣቅሳሉ፡፡ በአሜሪካና በአዉሮፓ በመንግስት ዕውቅና የተሰጣቸው በርካታ የግብረሰዶማውያን ማህበራት መኖራቸው እሙን ነው፡፡ በአውሮፓ ውስጥ ከፍተኛ ዕውቅናና ተቀባይነት ያላት የአንግሊካን ቤተክርስቲያን ተመሳሳይ ጾታን ማጋባቷና ዕውቅና መስጠቷ የሩቅ ጊዜ ታሪክ አይደለም፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአገራችን ኢትዮጵያ ግብረሰዶማውያኑ ዕውቅና እንዲሰጣቸው ጥረት ማድረጋቸው የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡ ከዚህም በላይ ደግሞ ወጣት ወንዶችና ተማሪዎች ተጠለፉና ተደፈሩ የሚሉ ዜናዎችንም በተለያዩ የመገናኛ አውታሮች በኩል መስማት ከጀመርን ውለን አድረናል፡፡ አገራችን ኢትዮጵያ የሕዝቧ ማህበራዊ፣ ሞራላዊና ሥነ-ምግባራዊ ሁኔታ አንፃራዊ በሆነ መልኩም ቢሆን ጥሩ እንደሆነ ይታመናል፡፡ ለዚህም ደግሞ ቤተክርስቲያን ከፍተኛውን አስተዋጽኦ እንዳደረገች እሙን ነው፡፡ ዛሬም ሕዝባችንን ከማህበራዊና ሞራላዊ ዝቅጠትና ቀውስ ለመታደግ መጽሐፍ ቅዱስን መመሪያዋ ያደረገች ትክክለኛዋ ቤተክርስቲያን ከፍተኛ ድርሻና ኃላፊነት አለባት፡፡
በዚህ አጭር ጽሑፌ የእግዚአብሔር ቃልና የቤተክርስቲያን ዋነኛ መመሪያ የሆነው፣ የሰውንም ሕይወት በመለወጥ ተወዳዳሪ ያልተገኘለት ታላቁ መጽሐፍ፤ መጽሐፍ ቅዱስ ከብሉይ እስከ አዲስ ኪዳን ድረስ ስለ ግብረሰዶምና ስለግብረሰዶማውያኑ ምን እንደሚል እንዲሁም ደግሞ ትክክለኛዋ ቤተክርስቲያን በጉዳዩ ሊኖራት የሚገባውን አቋም በጥቂቱ ለመዳሰስ እሞክራለሁ፡፡ ለዚህ ጽሑፌ የምጠቀመው መጽሐፍ ቅዱስ በኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር አሳታሚነት በ 1954 ዓ.ም. በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት የታተመውን በተለምዶ ²አሮጌው² ወይም የ²ድሮው² ተብሎ የሚታወቀውን መጽሐፍ ቅዱስ ነው፡፡ ይህን የመረጥኩበት አጭር ምክንያት በብዙ ኢትዮጵያውያን እጅ ስለሚገኝ ነው፡፡ ወደ ዋናው ጉዳይ እንግባ!
1. ኦሪት ዘፍጥረት ምዕ. 19
የዚህን ምዕራፍ ታሪክ ስንመለከት ሎጥ በሰዶም ይኖር በነበረ ጊዜ ሁለት መላእክት/ሰዎች ወደ ሰዶም ገቡ፤ ሎጥ ደግሞ በጥሩ የእንግዳ ተቀባይነት ባህሪው እነዚህን ሰዎች ይቀበላል፤ ወደ ቤቱም ያስገባቸውና ጥሩ መስተንግዶም ያደርግላቸዋል፡፡ እነዚህ መላእክቶች/ሰዎች ወደ ሎጥ ቤት መግባታቸውን ያዩ የከተማይቱ ሰዎች በዚያ ምሽት የሎጥን ቤት ከከበቡ በኃላ “በዚህ ሌሊት ወደ ቤትህ የገቡት ሰዎች ወዴት ናቸዉ ? እናውቃቸው (ሩካቤ ሥጋ እንፈጽምባቸው) ዘንድ ወደ እኛ አውጣቸው” (ቁ.5)፤ ብለው ሲያስጨንቁት ሎጥ ደግሞ “ይህን ክፉ ነገር አታድርጉ… ወንድ ያላወቁ ሁለት ሴቶች ልጆች አሉኝ፤ እነርሱን ላውጣላችሁ እንደወደዳችሁም አድርጓቸው” ብሎ ሲለምናቸው እናነባለን፡፡ ከዚያም ሰዎቹ የሎጥን ተማጽኖ እምቢ ብለው ቤቱን ሰብረው ለመግባት መታገላቸውን ከታሪኩ እንገነዘባለን፡፡ ከዚያ በኃላ የተከሰተውን በትኩረት ስንመለከት፡-
Ø መላእክቱ/ሰዎቹ ሎጥን ወደ ቤት በማስገባት ከሰዶም ሰዎች አዳኑት፣
Ø በቤቱ ደጃፍ የነበሩትን ሰዶማውያን ዓይናቸውን አሳወሩአቸው፣
Ø ሎጥና ቤተሰቦቹ ከከተማይቱ በፍጥነት እንዲወጡ አደረጓቸው፣
Ø በሰዶማዉያኑ ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ ተቀሰቀሰ፣
Ø እግዚአብሔርም በሰዶምና በገሞራ ላይ ከሰማይ እሳትና ዲን አዘነበ፤
Ø እግዚአብሔር ከተሞችን፣ በዙርያቸው ያለውንም ሁሉ፣ በከተሞቹ የሚኖሩትን ሁሉ፣ የምድሩንም ቡቃያ ሁሉ ገለበጠ (አጠፋ)፡፡
ከዚህ ጥቅስ ጠቅለል ባለ መልኩ የምንማረው፤ ግብረሰዶማዊነት እጅግ ክፉ ተግባር መሆኑን፣ የእግዚአብሔርን ቁጣ የሚቀሰቅስ መሆኑን፣ በጥቂት ግለሰቦች ክፉ ስራ በሕዝብና በአገር ላይ ሁሉ ከበድ ያለ ፍርድ የሚያመጣ፣ አገርንና ሕዝብን ለታላቅ ጥፋት የሚዳርግ አስጸያፊ ተግባር መሆኑን ነው፡፡
2. ኦሪት ዘሌዋውያን ምዕ. 18፡22 እና ምዕ. 20፡13
ለእስራኤላውያኑ ማህበራዊና ሃይማኖታዊ መተዳደሪያ ሕግ በሙሴ በኩል ከእግዚአብሔር ተሰጥቶአቸዋል፡፡ በእነዚህ ጥቅሶች በቀጥታ ግብረሰዶማዊነትን የሚፃረር ሕገ እግዚአብሔር ከእግዚአብሔር ተሰጥቶአቸዋል፡፡ ጥቅሶቹን በቀጥታ እንመልከት፡-
Ø ‹‹ከሴትም ጋር እንደምትተኛ ከወንድ ጋር አትተኛ ጸያፍ ነገር ነውና››(18፡22)፡፡
Ø ማናቸውም ሰው ከሴት ጋር እንደሚተኛ ከወንድ ጋር ቢተኛ ሁለቱ ጸያፍ ነገር አድርገዋል ፈጽመው ይገደሉ ደማቸው በላያቸው ነው(20፡13)፡፡
ይህ ሕግ ለእስራኤላውያኑ ብቻ የተሰጠ ሳይሆን ዛሬም መጽሐፍ ቅዱስን ዋነኛ መመሪያ ላደረገችው ቤተክርስቲያንም ሆነ የሕይወታቸውና የኑሮአቸው መመሪያ ላደረጉ አማኞች ሁሉ የሚሠራ ነው፡፡ ስለሆነም በእግዚአብሔርና በሰውም ፊት ጸያፍ ከሆነውና ከባድ ፍርድን ከሚያስከትለው የግብረሰዶማዊነት ተግባር፣ አገርና ሕዝብ እንዲጠበቅ ቤተክርስቲያን ድርሻዋን ልትወጣ ይገባል፡፡
3. ሮሜ ምዕ. 1፡18-32
| ወደ አዲስ ኪዳን ስንሻገር ደግሞ የሮሜ መልዕክት ጸሀፊ የእግዚአብሔር ቁጣ በሰዎች ላይ የሚገለጥባቸውን ዋና ዋና መንፈሳዊና ማህበራዊ ምክንያቶች በተጠቀሰው ክፍል ዘርዝሮአል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ አንዱ ግብረሰዶማዊነት ነው፡፡ ጥቅሶችን በቀጥታ እንመልከት፡- ስለዚህ እርስ በርሳቸው ሥጋቸውን ሊያዋርዱ እግዚአብሔር በልባቸው ፍትወት ወደ ርኵስነት አሳልፎ ሰጣቸው፤…ስለዚህ እግዚአብሔር ለሚያስነውር ምኞት አሳልፎ ሰጣቸው፤ ሴቶቻቸውም ለባሕርያቸው የሚገባውን ሥራ ለባሕርያቸው በማይገባው ለወጡ፤ |
| እንዲሁም ወንዶች ደግሞ ለባሕርያቸው የሚገባውን ሴቶችን መገናኘት ትተው እርስ በርሳቸው በፍትወታቸው ተቃጠሉ፤ ወንዶችም በወንዶች ነውር አድርገው በስሕተታቸው የሚገባውን ብድራት በራሳቸው ተቀበሉ።እንደነዚህ ለሚያደርጉት ሞት ይገባቸዋል የሚለውን የእግዚአብሔርን ሕግ እያወቁ እነዚህን ከሚያደርጉ ጋር ይስማማሉ እንጂ አድራጊዎች ብቻ አይደሉም(ሮሜ 1፡24፤26-27፤32)፡፡ |
እንግዲህ ከዚህ ክፍል በግልጽ እንደምንረዳው ግብረሰዶማዊነት ተፈጥሮአዊ ባሕርይ አይደለም፡፡ የእግዚአብሔርን ተፈጥሮአዊ ሕግ የሚጥስ፣ ርኩሰት የተሞላበት አስነዋሪ ተግባርና ከእግዚአብሔር ዘንድ ቁጣንና ፍርድን የሚያመጣ ተግባር ነው፡፡ ስለሆነም እንደዚህ ዓይነት ተግባር ከሚፈጽሙ ጋር አብሮ መፈጸም ቀርቶ ከሀሳባቸው ጋር እንኳ መስማማት በእግዚአብሔር ፈጽሞ የተከለከለ ስለሆነ ትክክለኛዋ ቤተክርስቲያን በምንም መንገድ ይህን ተግባር እንደ ሰዎች መብትና ነጻነት አድርጋ ልትቀበል አይገባም፡፡
4. 1ቆሮንቶስ ምዕ. 6፡9-10
ማህበራዊ ሞራላዊና ስነ-ምግባራዊ ችግር ለገጠማት የቆሮንቶስ ቤተክርስቲያን ሐዋሪያው ጳዉሎስ ከእግዚአብሔር መንግስት የሚያስቀሩ በርካታ ኃጢአቶችን ይዘረዝራል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ አንዱና የሰውን ልጅ አመጸኝነት አጉልቶ የሚያሳየው የግብረሰዶማዊነት ኃጥአት ነው፡፡ የሚከተለው ጥቅስ ይህንን እውነት በግልጽ ያስረዳናል፡፡
| ወይስ ዓመፀኞች የእግዚአብሔርን መንግሥት እንዳይወርሱ አታውቁምን? አትሳቱ፤ ሴሰኞች ቢሆን ወይም ጣዖትን የሚያመልኩ ወይም አመንዝሮች ወይም ቀላጮች ወይም ከወንድ ጋር ዝሙት የሚሠሩ |
| ወይም ሌቦች ወይም ገንዘብን የሚመኙ ወይም ሰካሮች ወይም ተሳዳቢዎች ወይም ነጣቂዎች የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም(1ቆሮ.6፡9-10)። የትክክለኛዋ ቤተክርስቲያን ትልቁ ተልዕኮ ለሰው ሁሉ የምስራቹን ወንጌል በመስበክ ሰዎች በክርስቶስ በኩል ከእግዚአብሔር ጋር ታርቀው የመንግስቱ ወራሾች እንዲሆኑ ማብቃት ነው፡፡ ስለሆነም የሰው ልጅን ከእግዚአብሔር መንግስት ከሚያስቀሩት አንዱና ዋነኛ የሆነውን የግብረሰዶማዊነትን ኃጢአት ትክክለኛዋ ቤተክርስቲያን አጥብቃ ልትዋጋ ይገባል፡፡ |
5. 1ኛ ጢሞቴዎስ ምዕ. 1፡9-11
ሐዋሪያው ጳውሎስ በዚህ መልዕክቱ፣ ሕግ የተሰጠበትን ዓላማ በመግለጽ ሐሰተኞች አስተማሪዎችን ወይም ደህና (መልካም) የሆነውን የወንጌል ትምህርት የሚቃወሙትን ሰዎች ባሕርይ ከማመልከቱም በላይ ሕግ የተሰጠበትን ዓላማ ያሳየናል፡፡ ጥቅሱን ልብ እንበል!
‹‹ይኸውም፥ ለበደለኞችና ለማይታዘዙ፥ ለዓመጸኞችና ለኃጢአተኞች፥ ቅድስና ለሌላቸውና ለርኵሳን፥ አባትና እናትን ለሚገድሉ፥ ለነፍሰ ገዳዮችና ለሴሰኞች፥ ከወንድ ጋርም ለሚተኙ፥ በሰዎችም ለሚነግዱ፥ ለውሸተኞችም በውሸትም ለሚምሉ፥ የብሩክ እግዚአብሔርንም ክብር እንደሚገልጥ ለእኔ አደራ እንደ ተሰጠኝ ወንጌል የሆነውን ደኅና ትምህርት ለሚቃወም ለሌላ ነገር ሁሉ ሕግ እንደ ተሰራ እንጂ ለጻድቅ እንዳልተሰራ ሲያውቅ ነው››(1ጢሞ. 1፡9-11)።
ስለሆነም እነዚህ ሰዎች ኅብረተሰባችንና ትውልዱን እንዳይበክሉ በፍቅርና በማቅናት አልያም በሕግ መጠበቅ ሀገራዊም፤ ክርሲቲያናዊም ግደታ እንደሆነ ልንገነዘብ ይገባል፡፡
6. 2 ጴጥሮስ ምዕ. 2፡2-10
ሐዋሪያው ጴጥሮስ ለሚጽፍላቸው ሰዎች አስቀድሞም ሆነ አሁን በሕዝቡ መካከል ሐሰተኞች ነቢያት እንደነበሩና እንዳሉ ከገለጸ በኋላ ክፉ ባሕርያቸውን ዘርዝሮ እግዚአብሔር ኃጢአትን ያደረጉትን መላእክት እንኳ ሳይቀር እንደቀጣቸው በመናገር ያስጠነቅቃቸዋል፡፡ በመቀጠልም ኃጢአትን በሚያደርጉት ሰዎች መካከል ጻድቅ የነበረዉ ሎጥ እንዴት እንደኖረ ይናገራል፡፡
| ጻድቅ ሎጥም በመካከላቸው ሲኖር እያየና እየሰማ ዕለት ዕለት በዓመፀኛ ሥራቸው ጻድቅ ነፍሱን አስጨንቆ ነበርና በዓመፀኞች ሴሰኛ ኑሮ የተገፋውን ያን ጻድቅ ካዳነ፥ |
| ጌታ እግዚአብሔርን የሚያመልኩትን ከፈተና እንዴት እንዲያድን፥ በደለኞችንም ይልቁንም በርኵስ ምኞት የሥጋን ፍትወት እየተከተሉ የሚመላለሱትን ጌትነትንም የሚንቁትን እየቀጣቸው ለፍርድ ቀን እንዴት እንዲጠብቅ ያውቃል። ደፋሮችና ኵሩዎች ሆነው ሥልጣን ያላቸውን ሲሳደቡ አይንቀጠቀጡም፤(2ጰጥ. 2፡7-10) |
ልክ እንደሎጥ በዚህ ዘመን የሚኖሩ የእግዚአብሔር ሰዎች (ቤተክርስቲያን) አስጻያፊ በሆነው የዓመፀኞች ሥራ ሳይወሰዱ በሚያድነው ጌታ በመታመን ጸንተው ሊቆሙ ይገባቸዋል፡፡ ከሚመጣውም ፍርድ ትውልድን የማዳን ኃላፊነት ከማንም በላይ የትክክለኛዋ ቤተክርስቲያን ነው፡፡
7. የይሁዳ መልዕክት ቁ. 7
ይሁዳ ለተደራስያኑ ይህንን መልዕክት በሚጽፍበት ጊዜ የእግዚአብሔርን ጸጋ አጥላልተው የሚያስተምሩና ሥነ-ምግባር የጐደላቸው አንዳንድ መምህራን ተነስተው ነበር፡፡ በዚህ መልዕክት ተደራስያኑ እንዲጠነቀቁና የተጣመመውን ትምህርት በሚያድነው የእግዚአብሔር ጸጋና የእውነት ትምህርት ለመቃወም እንድችሉ ያሳስባቸዋል፡፡
‹‹እንዲሁም እንደ እነርሱ ዝሙትን ያደረጉና ሌላን ሥጋ የተከተሉ ሰዶምና ገሞራ በዙሪያቸውም የነበሩ ከተማዎች በዘላለም እሳት እየተቀጡ ምሳሌ ሆነዋል››(ይሁዳ 7)።
እንግዲህ እስካአሁን በተመለከትናቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች መጽሐፍ ቅዱስ ምን ያህል ግብረሰዶማዊነትን አጥብቆ እንደሚቃወም መረዳት ችለናል ብየ አምናለሁ፡፡ ይህ ከሆነ ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስን የእምነቷና የሕይወቷ መመሪያ ያደረገችው ትክክለኛዋ ቤተክርስቲያን ይህንን የመጽሐፍ ቅዱስ ድምፅ ከፍ አድርጋ በማሰማት ትውልድንና አገርን ከአስከፊው የግብረሰዶማዊነት ከባድ ጥፋት ለመታደግ ቆርጣ ልትነሳ ይገባል፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ! ሕዝቧንም ከአስከፊው የሥነ-ምግባር ውድቀትና የግብረሰዶማዊነት ኃጢአት ይጠብቅ!! ለዛሬ አበቃሁ!